Tag Archive for: ፖለቲካ

በትግራይ ጦርነቱ አሁንም እንደ ቀጠለ ነው ሲል ተመድ ገለጸ

የተመድ ልኡካን አዲስ በለቀቁት ሪፖርት እንደገለጹት ከሆነ በትግራይ አሁንም አለመረጋጋቱ ቀጥሏል።

ሪፖርቱ እስከተጠናቀረበት ድረስ በመቀለ፣ ሽረና ሸራሮ ዙሪያ በበርካታ ቦታዎች ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው።  ልዑካኑ ወደ ሽረና ሽራሮ መጓዝ እንዳልቻለ ገልጿል።

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት  (UN OCHA) በታህሳስ ወር በሁለት ቡድን ወደ ትግራይ ተጉዞ ጥናት ካደረገ ብኋላ በለቀቀው ሪፖርት መሰረት፣ በጦርነት በተጎዳው ክልል ውስጥ ከ4.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የገለጸ ሲሆን፣ ከጦርነቱ ወዲህ የምግብ እርዳታ ያገኙ ሰዎች 100 ሺ እንደማይሞሉ ለማወቅ ተችሏል።

በተጨማሪም ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ 2.2 ሚሊዮን የክልሉ ኗሪዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን ጠቁሟል።

በፀጥታና በቢሮክራሲያዊ መሰናክሎች ምክንያት የከተማ አካባቢዎችን ብቻ ለመገምገም እንደተገደደ የገለጸው የልኡካን ቡድኑ፣ በክልሉ ውሱን የምግብ አቅርቦት እንዳለና ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እየታየ መሆኑን በሪፖርቱ አመላክቷል። የባንክ አገልግሎት ስለመጀመሩ የተገለጸ ነገር የለም።

የልዑካን ቡድኑ በጉብኝቱ “ደካማ የመንግስት አገልግሎቶች፣ አስከፊ የኑሮ ሁኔታ እና የሰብአዊ ጉዳዮች እንዳሉ” መታዘቡን በሪፖርቱ አመላክቷል ፡፡

በርካታ ንብረቶች እንደወደሙና እንደተዘረፉ ያመላከተው ሪፖርቱ፣ በክልሉ ከሚገኙ 40 ሆስፒታሎች ውስጥ በሽተኞችን በአካል ተቀብለው በማስተናገድ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት 5 ብቻ መሆናቸውን ገልጿል። ከነዚህ በተጨማሪ አራት ሆስፒታሎች የስልክ አገልግሎት ብቻ ይሰጣሉ ብሏል።

የኤርትራ ወታደሮችም በውጊያው መሳተፋቸውን የኢትዮጵያ መንግስት ሲክድ የቆየ ቢሆንም፣ የንግድ ተቋማትን በመዝረፍ እና ስደተኞችን አፍኖ በመውሰድ የኤርትራ ወታደሮች ተሰማርተው ማየታቸውን ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁ የእርዳታ ሰራተኞች እና ዲፕሎማቶች ገልጸዋል፡፡

የሰሜን እዝ አዛዥ ሜጀር ጄነራል በላይ ስዩም እና በፌደራል መንግስት የተሾመው ጊዜያዊው የመቀለ ከንቲባ አቶ አታክልቲ ወልደስላሴ በተናጠል ከመቀለ ኗሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ እንደሚገኙ ማመናቸው ይታወሳል።

ሰ.ነ. 

 

ፖለቲካዊ ሕጽቦ – ኢሳይያስ ኣፍወርቂ

እዚ ጽሑፍ’ዚ፡ ፕረዚደንት ኢሳይያስ ኣፍወርቂ፡ ብ11 ሓምለ 2018 ድሕሪ ቐትሪ፡ ኣብ ሳዋ፡ ንተሳተፍቲ 8ይ ሃገራዊ ፈስቲቫል መንእሰያት ንህልዊ ኵነታትን ምዕባለታትን ቀርኒ-አፍሪቃ ኣመልኪቱ ካብ ዘካየዶ ሰሚናር ተጸሚቚ ዝቐረበ እዩ። መበገሲ ናይቲ ሕጂ አብ ትግራይን አብ ቀርኒ-አፍሪቃን ዝረአይ ዘሎ ቅልውላው እንታይ ክኸውን ከምዝኽእል ዝሕብር ጽሑፍ ኮይኑ ስለዝረኸብናዬ ክተንብብዎ አብዚ አቅሪብናዬ አለና። Read more

ትርጉም የለሽ ምጥ የለም!

አብይ አሕመድ (መሽሬ) ስልጣን እንደያዘ በጥቂት ሳምንታት የህወሓት ባለስልጣናትን ከ4ኪሎ ሲያጸዳ፣ የፓርቲ ፖለቲካ ነበር። ያኔ እኔን ጨምሮ ብዙ ትግራዋይ ግድ አልሰጠንም ነበር። እንዲያውም አብዛኛው ትግራዋይ እንደማንኛውም የተቀረው ህዝብ በደስታ የሰከረበት ግዜ ነበር።
መሽሬ ኢህአዴግን አፍርሶ ህወሓት የሌለበት ብልጽግናን ሲመሰርትም የፓርቲ ፖለቲካ ነበር። የፌደራል ስርዓቱ ሲምቦል ተደርጎ የሚወሰደው የድርቶች ስብስብ/ግንባር፣ ተጨፍልቆ ወጥ መሆኑ ፌደራላዊውን ስርዓት አፍርሶ አሃዳዊ ስርዓት ለመተካት የሚደረግ ርብርብ መስሎ የታየው (ትግራዋይን ጨምሮ ሌሎች የብሔር ፖለቲካ አራማጆች) ስጋቱን ከመግለጹ ውጪ፣ ከፓርቲዎች ሽኩቻ ነጥሎ የሚያይበት ምክንያት አልነበረውም።
ትግራይንና ህወሓትን ያገለለ የኢትዮ ኤርትራ ግኑኝነት ግን ከፓርቲ ፖለቲካ በላይ ነበር። የኢሳያስ የመጨረሻ ግብ በቀል እንደሆነ እያንዳንዱ ትግራዋይ ጠንቅቆ ያውቃል። ትግራይን ያገለለው ሽርጉድ ህልውናው ላይ እንደተጋረጠ አደጋ ቆጥሮታል፣ ከዴይ ዋን ጀምሮ።
ከአመት በላይ የዘለቀው የአማራ የመስፋፋት ፍላጎትና ጦር ጉሸማም ከፓርቲ ፖለቲካ በላይ ነበር። የትግራይ ህዝብ እንደ ኤግዚስቴንሻል ትሬት ያየበት፣ በላይ በኤርትራ በታች በአማራና በስልጣን ፈላጊ ምንደኞች ተቀርቅሮ በእሳት ሊለበለብ እንደሚችል አስቀድሞ ተገንዝቧል።
ለዚህም ህዝቡ ህልውናውን ቀስ በቀስ ከፓርቲው ህልውና ጋር አቆራኝቶ ማየት ጀመረ።
መሽሬ ስልጣኑን በህገወጥ መንገድ አራዝሞ ሌሎችም ምርጫ እንዳያካሂዱ ሲያግድ፣ የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አፈንግጦ ምርጫ አደርጋለሁ ሲል በእርግጥ የፓርቲ ፖለቲካና የስልጣን ሹክቻ ጉዳይ ነው። ነገር ግን ከዛም በላይ ነው፤ የህገመንግስታዊ መብት፣ የሉአላዊነትና የህልውና ጉዳይ ነው።
ፌደራል መንግስት እውቅና አልሰጥም እያለ፣ ህገወጥ ነው እያለ፣ የክልሉ መንግስት ምርጫ አካሂዷል። ህዝብም ተገዶ ሳይሆን ወዶና ፈቅዶ በአደባባይ እየጨፈረ በምርጫ ተሳትፏል። በነበረው የአገሪቱ ሁኔታና የህዝብ ስጋት፣ ህዝቡ ህልውናዬን፣ መብቴን፣ ጥቅሜን ከሌሎች በተሻለ ያስጠብቅልኛል ብሎ ላመነው ድርጅት ድምጹን ሰጥቷል።
እዚህ ላይ ህዝቡ ሁለት ሀላፊነቶችን willingly እንደወሰደ ልብ እንበል፤ አንደኛ የፌደራል መንግስቱን ትዕዛዝ አልቀበልም ብሏል። ሁለተኛ የሚበጀኝን የመምረጥ ህገመንግስታዊ መብቴን እጠቀማለሁ ብሎ የሚበጀውን መርጧል።
ከዚህ ብኋላ ያለው ጉዳይ በሙሉ የፖርቲ ፖለቲካ ሳይሆን የህዝብና የሉአላዊነት ጉዳይ ሆኗል።
ከ2ሚልዮን በላይ ድምጹን የሰጠበት ምርጫ ማንም በምንም መንገድ ሊሰርዝ ሊደልዘው አይችልም። ተገድጄ ነው የመረጥኩት ካላለ፣ ለመገደዱ ማስረጃ ከሌለ፣ በስተቀር ማንም ሰው/ሀይል በምንም መንገድ የህዝቡን ውሳኔና የወሰደውን ሃላፊነት መደለዝ አይችልም። አራት ነጥብ።
ከምርጫው ብኋላ ህጋዊ ክልላዊ መንግስት ነኝ፣ ሳይመረጥ የፌደራል መንግስት ነኝ ለሚለው ህገወጥ ቡድን እውቅና አልሰጥም ሲል፣ የፌደራል “መንግስት”ና የክልሉ መንግስት መውጫ የሌለው ቅርቃር ውስጥ እየገቡ ነበር። አብሮ መስራት አይቻልም። ሁሉንም ያሳተፈ አገር አቀፍ ድርድር አድርጎ ችግሮችን ለመፍታትም የፌደራሉ ማፊያ ቡድን ፍላጎት አልነበረውም። (የኦሮሚያና የአዲስ አበባ ተቀናቃኞቹን ማሰር ችሎ ስለነበር፣ ስልጣኑን ለመቆጣጠር ከግማሽ መንገድ በላይ የተጓዘ መስሎታል። Why’d he retreat?)
እንደመፍትሔ የወሰደው እኔም ለክልሉ መንግስት እውቅና ስለማልሰጥ ግኑኝነቴን በቀጥታ ከወረዳ ጋር አደርጋለሁ የሚል ነበር። ዳሩ ግን እስከ ቀበሌ ድረስ ያለው መንግስታዊ መዋቅር፣ የክልሉን መንግስት የተቆጣጠረው ፓርቲ ነው ያለው። ከወረዳዎች ጋር በቀጥታ ሊገናኝ የሚችልበት አጋጣሚ አለነበረም። ግኑኝነታችን ከክልሉ መንግስት ጋር ነው የሚል ምላሽ ነበር የሚያገኘው።
እዚህ ቅርቃር ውስጥ የገባው የፌደራሉ ማፊያ፣ ለክልሉ መንግስት እውቅና ስለማይሰጥና ወረዳዎችም በቀጥታ ለመገናኘት ሀላፊነት መውሰድ የማችሉ ስለሆኑበት፣ በጀቶችን መቁረጥ፣ የህክምና ቁሳቁስ አለመላክ፣ እርዳታ ማስቀረት፣ ወዘተ አይነት እርምጃ ገባ። ህዝቡም ህገወጥ ነው እየተባለ ምርጫ ተሳትፎ ድምጹን ስለሰጠ፣ አብሮ መቅጣት እንደ አምራጭ ታዬ።
ጉዳዩ የፖለቲካ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሉአላዊነት ጉዳይ እየሆነ መጣ። የህዝብ አጀንዳ ሆነ።
በዚህ መልኩ ሊቀጥል እንደማይችል ሲያውቅ ቀድሞ ሲዘጋጅበት የቆየውን በጉልበት የማንበርከኩን አማራጭ ገፋበት። አቅሙን ፈተሸ። የኤርትራን አቅም ፈተሸ። ኢሳያስን ጋብዞ አቅሙን አሳየ። በተቀናጀ መልኩ ጦርነት ለመክፈት ዝግጅቶች ተጠናቀቁ።
የሰሜን እዝ አዛዥ ለመቀየር ሞከረ፣ የክልሉ መንግስት ከለከለ።
ዘ ሬስት ኢዝ ሂስትሪ።
ጦርነት ክልሉ ላይና ህዝቡ ላይ ሲከፈት፣ ህግ የማስከበር ጉዳይ፣ በህግ የሚፈለጉ ግለሰቦች የመያዝ ጉዳይ ወይም የፖለቲካ ፓርቲ ጨዋታ አይደለም።
በተለይ ደግሞ የውጭ ሀይሎችን አሳትፎ፣ የተለያዩ በቀል የተጠሙ ቡድኖች አሰባስቦ፣ በሰማይና በምድር ደግሞም ሁሉም አቅጣጫ እሳት እየለቀቁ የገቡበት ጦርነት፣ የህወሓት ባለስልጣናትን ከ4 ኪሎ ሲያባርሯቸው እንደነበረው አይነት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጨዋታ አይደለም።
ወገኖቻችን ያለቁበት፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የተፈናቀሉበት፣ እናቶቻችንና እህቶቻችን የተደፈሩበት፣ ንብረቶቻችን የወደሙበትና የተዘረፉበት፣ ከተሞቻችን የበረሱበትና በጄኖሳይድ ንጹሀን የተጨፈጭፉበት፣ ትግራዋይነት ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው።
በህግ የሚፈለጉ የግለሰቦች ጉዳይ አይደለም። የፖለቲካ ፓርቲዎች ጉዳይ አይደለም። እንደኮንቬንሽናል ዋር የአንድ ትውልድ ጉዳይም አይደለም። የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው!
ይህን ሁሉ እያደረጉም፣ ሲቪልያን ከጦር ቀጠና እንዳይሸሹ መንገድ ዘግተው፣ መላወሻ አሳጥተው፣ ንብረታቸውን እየዘረፉ፣ ቀለባቸውን እየተናጠቁ፣ ከአለም ነጥለው፣ የደረሰባቸውን ግፍ እንዳይገልጹ፣ ሮሯቸውን እንዳያሰሙ፣ ቆልፎ መቀጥቀጥ፣ የፓርቲ፣ የግለሰብ፣ የአንድ ትውልድ ጉዳይ አይደለም።
ለዚህም ነው እያንዳንዱ ጤነኛ ትግራዋይ ይህን በማንነቱ ላይ የተቃጣ የዘር ማጥፋት ዘመቻ በጋራ ለመመከት በጋራ መቆም ያለበት።
ትግራይ ምጥ ላይ ነች።
አንዳንዶች ትርጉም የለሽ ጦርነት ነው ይላሉ። እናት ትርጉም የለሽ ምጥ አምጣ አታቅም። እናት የምታምጠው ለመውለድ ነው። ትግራይ ነጻ ሀገርን ለመውለድ እያማጠች ነው።
ማርያም ጽዮን ብሽልምትኺ ተውፅእኪ ንበላ። ንደግፋ! ኩልና ንረባረብ!

ሶስቱ የጥፋት ፈረሶችና የኢትዮጵያ ፍጻሜ!

ከዚህ ጦርነት ብኋላ፣ መደምደሚያው ምንም ይሁን፣ ኢትዮጵያ እንደ አገር የመቀጠል እድሏ ዜሮ ሆኗል። አክትሞላታል። ህወሓት ጦርነቱን ቢያሽንፍ እንኳን ተመልሶ አገር በማስተዳደር ረገድ ከእንግዲህ ድርሻ ይኖረዋል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ህዝቡም ህወሓትም ያንን እድል/ሁኔታ ዳግም የሚፈልጉት አይመስለኝም። ባንዳዎቹና ግልገሎቹ ከቀናቸውም ኢትዮጵያን ማስቀጠል አይችሉም። ዝርዝሩን አቀርባለሁ።

የኦሮሚያ ብልጽግና፣ የአማራ ብልጽግናና የሻዕቢያ አላቻ ጋብቻ በልጅነቴ እየሰማሁት ያደግሁት የዘንዶ ታሪክ ያስታውሰኛል። እነዚህ ሶስቱ ሀይሎች በተናጠል ከህወሓት አንጻር ሲታዩ ቁጫጭ ናቸው። በጋራ ካልሆነ በተናጠል ህወሓትን መሞከር ቀርቶ ማሰብ የማይታሰብ ነው። ጋብቻቸው ስትራቴጂካል ነው፤ በቅድሚያ በጋራ ተረባርበው ይጥሉታል፣ አንደኛው ለስልጣኑ፣ ሁለተኛው ለመሬቱ ሶስተኛው ለበቀል። ሶስቱም ግን ሌላ የሚያመሳስላቸው አንድ ወሳኝ ባህሪ አለ። ሶስቱም ኤክስፓንሺንስት/ተስፋፊ ና ኦፖርቹኒስቲክ ናቸው። በለስ ቀንቷቸው ህወሓትን ካስወገዱ ወይም ያስወገዱ ከመሰላቸው፣ በማግስቱ ሌላ የመስፋፋትና እርስ በእርስ የመዋዋጥ ጌም ይጀምራሉ፥

1 የኦሮሚያው ብልጽግና ሁለቱን የሚፈልጋቸው ለሚቀጥሉት አስርት አመታት ስልጣን ላይ ለመቆየት መጠቀሚያ ለማድረግ ነው። ካልጠቀለላቸው ይህን ማሳካት አልችልም ብሎ ነው የሚያስበው። ከእርሱ ፈቃድ ውጪ መግባትና መውጣት የማይችሉ፣ ወዶና ፈቅዶ ብቻ ስልጣን የሚሸነሽናቸው አሻንጉሊቶች መሆን የግድ አለባቸው። አለበለዚያ የቀድሞ ጓዶቻቸውን ጉድጓድ ይጋራሉ። በሀሳብ ደረጃ፣ ሶማሊያን፣ ጅቡቲ፣ ኤርትራን፣ ሱዳንን ጠቅልለን በምስራቅ አፍሪካ ታላቅ “አገር” በገዳ አምሳል እንመሰርታለን የሚል ጽንፍ የረገጠ ተስፋፊ አጀንዳ ይዞ የተነሳ ቡድን መሆኑ አይዘነጋም።

2 የአማራ ብልጽግና የመሬት ይገባኛል ጥያቄ በወልቃይትና በራያ አይመለስም። በሰሜን በኩል አሰብን ይጠይቃል። ዳር ድንበሬ ቀይ ባህር ድረስ ነው ይላል። ከኦሮሚያም ሰፋፊ የሚጠይቃቸው ግዛቶችና ከተሞች አሉት። በድሮዋ የኢትዮጵያ ካርታ የሚታየው የአገሪቱ ክፍል በጠቅላላ የአማራ ግዛት ነው፤ የአማራ መሬት ነው ብሎ ያምናል። ጠንካራ ኢኮኖሚና ጠንካራ ሰራዊት በመገንባት ማእከሉን ዳግም መቆጣጠር ይፈልጋል። ወይም መቆጣጠር አለብኝ ብሎ ያስባል። ካለበለዚያ ህልውናው ሁሌም አደጋ ላይ እንደወደቀ ይሰማዋል። እየተሽሎከልለከና በሁለት ሶስት ፓርቲዎች እየተደራጀ ጡንቻውን ማፈርጠም ከህዝብ ያልተሰወረ ስልቱ ነው።

3 ኢሳያስ ህወሓት በተወገደ ማግስት ከኋላ ሆኜ እዘውራለሁ፣ ኢትዮጵያን በእጃዙር እገዛለሁ ብሎ ነው የሚያምነው። እየኮረኮመ የሚያሰራውን ከመጋረጃው ጀርባ በቡችላው አብይ አማካኝነት መሾም መቻል ይሆናል ነው ምኞቱ። ካልሆነ ከወዲ ዜናዊ ጋር የተጀመረው ጸብ በሲዝን ሁለት ይቀጥላል።

አስተዋላችሁ? በመካከላቸው እርስ በእርሳቸውም ሆነ፣ ከነሱ ውጪ ካለው ቡድን ጋር በእኩልነት መኖር የሚያስችል አጀንዳና የስነልቦና ቅድመዝግጁነት የላቸውም። ባህሪያቸው አንዱ ሌላኛውን ውጦ መዘንደድ ነው። ህወሓት በክልል ቆራርጦ ኢትዮጵያን ቢያሳንሳትም፣ በህግ አውቶኖሚውን ለክልሎች ሰጥቷል። ተጠቅመውበታል አልተጠቀሙበትም ሌላ ጉዳይ ሆኖ፣ ካልተመቻቸው እስከመገንጠል ድረስ ልዩ መብት የሚያጎናጽፍ ህገመንግስት ሰጥቷቸዋል። ትናንሽ ግን አውቶኖመስ የሆኑ የፖለቲካ ዩኒቶች (ክልሎችና ልዩ ዞኖች) በእኩልነትና በመፈቃቀድ የተመሰረተ አብሮነት ሲኖራቸው ብቻ አገር በጋራ ያስቀጥላሉ፤ ተብሎ ለ30 አመታት (ግማሹ የኢትዮጵያ ህዝብ የተመረተበት አመታት) ተሰርቶበታል። ኖረውበታልም።

ገሚሱ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ የአስተዳደር ሲስተም ውጪ ሌላ የሚያውቀው ነገር የለም። እንደ አይንአር በአንዴ ጠርገህ ልታጸዳውና ሊረሳ የሚችል ጉዳይ አይደለም። እናም በማዕከላዊ መንግስት ይሁንታና ፈቃድ የሚሾሙ የሙስጠፌ፣ የተመስገን ምናምን አይነት ታማኝነታቸው ለአንድ ግለሰብ የሆኑ መሪዎችና ለይስሙላ ብቻ የሚሰየሙ ምክር ቤት ይኖራችኋል፣ ቢባሉ ማናቸውም አሜን ብለው አይቀበሉትም። የቀመሷት ነገር አለች የምትጥም፣ የምትጣፍጥ። ማንነቴን፣ ባህሌን፣ ቋንቋዬን፣ እምነቴን፣ የሚሏት ነገር።

አንዱ ሌላኛውን ሰልቅጦ ለመዘንደድ ሲቧጨቁ፣ ሌላው ለማንነቱ ሲንተጋተግ፣ ሰላም፣ መረጋጋት፣ ልማት፣ አገር፣ ብሎ ነገር ፈጽሞ ያከትምለታል።
ድሕረ ህወሓት የምትኖረው ኢትዮጵያ የፈራረሰች ኢትዮጵያ ብቻ ናት። የታሪክ መጻህፍት ላይ ብቻ የምታገኟት። ፍጻሜዋ ያላማረ። በ21ኛው ክፍለዘመን በእርስ በእርስ ጦርነት እስከዘላለሙ ያሸለበች ኢትዮጵያ።

ይህ እንዳይመጣ ነበር፣ በድርድርና በውይይት አብሮ የሚያኗኑር መላ ፈልጉ፤ ካቃታችሁ ያለው የፌደራሊዝም ስርዓት ይቀጥል ወይስ በሌሎች አማራጮች (ጂኦግራፊ መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝም፣ ፍጹም አሃዳዊ ወዘተ) እንተካው ብላችሁ ህዝቡን ጠይቃችሁ በሪፈረንደም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ያግኝ፤ ብለን ስንመክራችሁ የኖርነው። በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተና የብዙሃን ይሁንታ ያገኘ ስርዓት ከመመምስረት ውጪ ሌላ አምራጭ የላችሁም ስንላችሁ የኖርነው በምክንያት ነው። ኢትኒክ ፌደራሊዝም በጉልበት ተጭኖ ሙሉ ተቀባይነትን እንዳላገኘ ሁሉ፣ አሃዳዊ ስርዓት በጉልበት ተጭኖ ሙሉ ተቀባይነትን አያገኝም። ግማሹን የህበረተሰብ ክፍል ያገለለ ስርዓት ደግሞ መቼም ቢሆን አይጸናም። እናም ከወዲሁ እላለሁ …

ነፍስ ይማር!

ሰ.ነ

 

ጎራችሁን ለዩ፥ ከህዝብ ወገን ወይስ ከወንጀለኞች ጎን

ሰለሞን ነጋሽ

ጦርነቱ ትክክል ነው፣ ከህወሓት ጋር ነው። ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ የሚደረግ ህግ የማስከበር ስራ ነው። ብላችሁ ለምታምኑ ህሊናችሁን እንድትፈትኑት የሚጋብዝ ጽሁፍ ነው። 95 ሚልዮን ለ5 ሚልዮን፣ ይጥፉ ወይስ እንጥፋ፣ ወዘተ በሚል የታወረ እይታ የምታራምዱ ከሆነ፣ ይህን ማንበብ አይመከረም እዚሁ አቁሙ። አላማው ምን ያህሉ በተሳሳተ መረጃ፣ የተሳሳተ አቋም እንደያዘ ለማወቅ ነው። ሁላችንም አቋማችንን እያጠራን እንድንሔድ ይረዳናል።

  1. ህወሓት አታልሎም ይሁን አሳምኖ የትግራይን ህዝብ ከጎኑ አሰልፏል። የትግራይ ህዝብ በፌደራል የተላለፈውን ህግ እያወቀ የክልሉ መንግስት ባዘጋጀው ምርጫ ተሳትፏል። ህወሓትንም መርጧል። የህዝብ ውሳኔ ምን ማድረግ ይቻላል?
  2. አብይ አሕመድ በሁሉም ቦታ ተቀባይነቱን የሚሸረሽር ስራ ሲሰራ ላለፉት ሁለት አመታት ቆይቷል። ኦሮሞው አልተቀበለውም። አማራው እንደ ፔንዱለም ቢወዛወዝም የተቃወመውና ያማረረበት ጊዜ ይበጣል፣ አዲስ አበቤው አልተቀበለውም፣ ወላይታ ሲዳማ ጉራጌ ወዘተ ሁሉም ከአብይ መንግስት ጋር አልተስማሙም። የትግራይ ለብቻው አይደለም። ይህ እውነታ ሰፊ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ሳያስፈልገው የትግራይ ህዝብ በራሱ ጊዜ ከህወሓት ጎን እንዲሰለፍ ዋነኛ ምክንያት ሆኗል። ወዶና ፈቅዶ ከጎኑ ከተሰለፈ ደግሞ እኔ አውቅልሀለሁ አይባልም። ፋሽሽታዊ ባህሪ ነው።
  3. በህገወጥ መንገድ ያለበቂ ምክንያት አብይ አሕመድ ስልጣኑን በራሱ መንገድ አራዝሟል። በዚህ ምክንያት ከህወሓት ጋር ብቻ ሳይሆን፣ ከሌሎች የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጋር መግባባት አልቻለም። በሀሰት ክስ ሁሉንም አስሯቸውም ይገኛል። በተለይ ልደቱ አያሌውን ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ ነጻ ቢለውም፣ ፈጽሞ ሊፈታው አልፈለገም። ከመስከረም 30 ብኋላ ሰላም እንደማይኖር በመናገሩ ብቻ ቂም ቋጥሮበታል። ልደቱ እንዳለው ታድያ የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደረሰን አየን እንጂ፣ ግምቱ የተሳሳተ አልነበረም። (“አደባባይ ውጡ አልል፣ ተኩሱ አልል፣ ምንም አልልም። ዝም ብዬ ነው የማየው” እንዳለው፣ ይኸው እርሱ ምንም ሳይል እኛ ጥቅምት ሳይገባደድ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሰናል ።)
  4. በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ግጭቶች ተስፋፍተዋል። ህወሓት ላይ ማሳበብ እንደማይቻል ባለፉት ጥቂት ቀናት ብቻ ያየናቸው ተደጋጋሚ ግጭቶች በቂ ማስረጃዎች ናቸው። ትግራይ ከተከበበች፣ ኔትዎርክ ከተዘጋና ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ በሌላ የአገሪቱ ክፍል የሲቪልያን ህይወትን የቀጠፉ ቢያንስ አምስት ግጭቶችን አይተናል። በህወሓት ማሳበብ አይቻልም።
  5. ኢሳያስን እየጋበዘ የጦር መሳሪያ ሲያስጎበኝ፣ አየር ሀይሉን ሲያሳይ፣ ለራሱም ኤርትራ ሄዶ አንዳንድ ሁኔታዎችን ሲያጠና፣ ወሎና ጎንደር ሄዶ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ እንደከረመ ሁላችንም እናውቃለን። ከህዝብ የተደበቀ እውነታ አይደለም። በራሱ ሚድያ የዜና እወጃ ሆኖ ሰምተነዋል/አይተነዋል። የገንዘብ ቅየራው፣ ወታደሩን ማጓጓዝ፣ ወታደራዊ አመራሩን መቀየር ወዘተ የጦርነት ቅድመ ዝግጅቱ አንድ አካል ነበሩ።
  6. ጦሩን አጓጉዞ፣ ከነ ኢሳያስ ጋር መክሮ፣ ተዘጋጅቶበት ሲያበቃ፣ ኋላ እንደተረጋገጠው በኦሮሞ ነጻ አውጪ ታጣቂዎች የተወሰደውን እርምጃ ህወሓት ላይ ለድፎና ያንን ሰበብ አድርጎ “ምክር ቤቱ”ን በማላቀስ ሲያስወስን የዋለ እለት፣ ጦርነቱን የሚጀምርበት ሁኔታን እያመቻቸው እንደነበር እንገነዘባለን። (ህወሓት የሰሜን እዝ ላይ እርምጃ ወሰደ ስልሚባለው ወሬ ሰለማያግባባን እንተወው። ኦፕሬሽኑን ቀድሞ የጀመረው አማራና ሶማሌ ክልል ላይ እንዳደረገው በአውሮፕላን ኮማንዶ ጭኖ በመላክ የሞከረ ሲሆን ያ ሀይል ላይ ነው እርምጃ የተወሰደው፣ የሰሜን እዙ ከጎናችን ተሰልፏል ባይ ነው ህወሓት። እርሱ ደግሞ እዛ ሲጠብቁ የነበሩትን በተኙበት ወጓቸው ነው የሚለው። ተጣርቶ ማስረጃው እስኪወጣ ድረስ ማንም ሰው እርግጠኛ ሊሆን አይችልም። ለፎቶ ካለው ፍቅር አንጻር ማስረጃ ቢኖረው ኖሮ ይፋ ያደርገው እንደነበር ግን ማስታወስ ያስፈልጋል። )
  7. ጦርነቱ በይፋ ከመጀመሩ በፊት ህዝቡ ላይ የተፈጸሙ ግፎችን በቅድሚያ እንመልከት፥ በጀት መከልከል። የዓለም ባንክና የመሳሰሉ አለም አቀፋ ተቋማት የሚሰጡትን እርዳታ መከልከል። ከስፖርት ውድድር ተጋሩን ማግለል። የኮቪድ ቁሳቁስ ወደ ትግራይ አለመላክ። ከውጪ የተገዙ የተለያዩ ቁሳቁሶች ወደ ክልሉ እንዳይገቡ ማገድ። መንገድ መዝጋት። ነዳጅ እንዳይገባ ማድረግ። በሁሉም ዙሪያ ክልሉን መክበብ። ጦርነት ከከፈተ ብኋላ ደግሞ ተደጋጋሚ የአየር ድብደባ በከተሞች ጭምር ማካሔድ። ከቤታችሁ እንዳትወጡ እደበድባለሁ ብሎ በአደባባይ ማወጅና ህዝብን ማሸበር። ከትግራይ ውጭ ያሉ ተጋሩን ማዋከብ፣ ኢትኒክ ፕሮፋይሊንግና ድንገተኛ ፍተሻ ተጋሩ ላይ ማካሔድ። በጸጥታ መዋቅር ውስጥ የነበሩ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ከስራ ማገድ፣ ትጥቃቸውን ማራገፍ፣ ብሎም ማሰር። ተማሪና የውጭ ዜግነት ያላቸው ተጋሩ ጭምር ወደ ውጭ እንዳይወጡ ማገድ። ከትምህርት፣ ከስራ፣ ከቢዝነሳቸው ማስተጓጎል። ወዘተ
  8. በብሔር የተደራጀ ልዩ ሀይልና ምልሻ እዚህ ጦርነት ውስጥ እንዲገባ አድርጓል። ወደ ብሔር ግጭት ሊያመራ ይችላል የሚል ስጋት በስፋት አለ።
  9. የውጭ ሀይል ማለትም የኤርትራና (ዛሬ ደግሞ የሱዳንም ተጨምሮበታል እየተባለ ነው) ጦርነቱ ውስጥ ጎትቶ ማስገባት።
  10. ለአለም አቀፍ የተኩስ አቁሙ ጥሪ ጆሮ አለመስጠት።

ይህ ሁሉ የተደረገውና እየተደረገ ያለው ጥቂት በህግ የሚፈለጉ ሰዎችን ለመያዝ ወይስ ትግራዋይን ለመስበር? የፈለገውን ያህል ኪሳራ ያስከትል (ትግራዋይ ተሰብሮም ይሁን) ደንታ የለንም ከሆነ መልሳችሁ አንድ ነገር ነው። ጥቂቶችን ለህግ ለማቅረብ ይህን ያህል ርቀት መጓዝ ትክክልና ተገቢ ነው ብላችሁ ከሆነ የምታምኑትና እርምጃውን የምትደግፉት ዝምታችሁ መልስ ይሆናል። እንደነ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው “የለም ይህ ትክክል አይደለም፣ እብደት ነው” የምትሉ ከሆነ ደግሞ አቋማችሁን አጥርታችሁ ይህን ጦርነት ለማስቆም ጫና መፍጠር ይጠበቅባችኋል።

በበኩሌ አብይ ህግ አስከባሪ ሆኖ በህግ ሊፈልጋቸው የሚችሉ ወንጀለኞች ይኖራሉ ብዬ አላምንም። ምናልባት የኢትዮጵያ ህዝብ እርሱንና ጋሻ ጃግሬዎቹን ወደ ህግ ማቅረብ የሚፈልገውን ያህል ከህወሓት ባለስልጣና ሌሎችም በህግ ሊጠይቃቸው የሚፈልጋቸው ሊኖሩ ይችላሉ። አሉም። ነገር ግን አብይ ከነሱ ተሽሎ ህግ አስከባሪ ነኝ የሚልበት ምንም የሞራል መሰረት የለውም ብዬ አምናለሁ። በደም የተጨማለቀ በብዙ ወንጀል የሚፈለግ፣ በገለልተኛ አካል ብዙ መጣራት ያለባቸው የህዝብ ጥያቄዎች አሉ። የአማራ መሪዎች ሞት፣ የኢንጅነር ስመኘው ግድያ፣ የነጄነራል ሰዓረ ሞት፣ የአርቲስት ሀጫሉ ግድያ፣ የዜጎች በየቦታው መፈናቀል በየተለይ አዲስ አበባ ዙሪያና ኦሮሚያ፣ የንጹሀን ዜጎች በየቦታው መሞትና ሌሎችም ሁሉም በገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን ተጣርተው ወንጀል ፈጻሚዎች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው። አገሪቱ አሁን የገባችበትን ጦርነት ጀስቲፋይ የሚያደርግ በቂ ምክንያት ስለሌለ፣ ወደ ጦርነት የከተቱን  ተጠያቂ ሰዎች ተጣርቶ ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል። እስከዛው ያለ በቂ ምክንያት የተገባው ጦርነት አንድን ሉአላዊ ህዝብ ለማንበርከክ የተቃጣ ወረራና ጥቃት ነው ብዬ ነው የማምነው። ለዚህም ነው ከትግራዋይ ወገኔ ጎን የቆምኩት። ተሳሳትኩ?

ከአርቲስት ሀጫሉ ግድያ በስተጀርባ ….

… በሆነው ነገር ከማዘን በላይ ተበሳጭቼ፣ ምንም ላለማለት ወስኜ ነበር። ነገር ግን ዝምታዬም ያስወቅሰኝ ጀምሯል። ታድያ … የሚሰማኝን ልጻፍና …

በቅድሚያ አንድ ነገር ልበል። በዚህ እድሜው በሰው እጅ ቀርቶ በበሽታም መሞት የማይገባው ወጣት ነበር አርቲስት ሀጫሉ። በፖለቲካ አመለካከቱ ባንግባባም፣ የሚያወራው ባይጥመኝም፣ ምናምን የሚል ቅራቅንቦ አልደርትም። ምንም ይሁን ምን ግድያውን ፍጹም አወግዛለሁ!! ገዳዮቹና አስገዳዮቹ (ህግ አስከባሪ የለም እንጂ) ለህግ ቀርበው የእጃቸውን ማግኘት እንዳለባቸውም አምናለሁ። በዚህ አጋጣሚ በአርቲስት ሀጫሉ ሞት፣ በሀዘን ልባቸው ለተሰበረ በሙሉ (አስመሳዮች የአዞ እንባ የሚያነቡትን ሳይጨምር) መጽናናትን ከልብ እመኛለሁ። እንዲህውም ከግድያው ብኋላ በተፈጠረ ቀውስ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች ሀዘኔ ጥልቅ ነው። ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ።

እንግዲህ ከሀጫሉ ግድያ በስተጀርባ ማን ሊሆን እንደሚችል ብዙ መላምቶችን ከተለያዩ አቅጣጫዎች እየሰማን ነው። ሞቱን ተከትሎም ሁሉም በየአቅጣጫው ለፖለቲካ ፍጆታው እየተጠቀመበት ነው። ለፖለቲካ ፍጆታ እንደሚውልና አመጽ እንደሚያቀጣጥል የሚጠበቅ ነበር። ለጊዜው መንግስት ነኝ የሚለው የአብይ ቡድን፣ ገዳዮቹ እነማን እንሆኑ እያጣራን ነው ባለበት ቅጽበት፣ ህወሓት ነው፣ ግብጽ ነው፣ የግብጽ ተላላኪዎች ናቸው፣ የሚሉ የተለያዩ ግራ የገባቸው ውንጀላዎችን ሰንዝሯል። ህግ ይዞታል ከተባለ፣ ተጣርቶ ሳያልቅ እንዲህ አይነት ውንጀላ፣ መነሻውና ጥቅሙ ምንድን ነው? የዛሬ ሁለት አመት፣ የምርመራ ውጤቱ ከመታወቁ በፊት ህወሓት ነው ከዚህ በስተጀርባ ያለው ብሎ የከሰሰው መሪ፣ ውጤቱ ሲታወቅ እስከዚች ደቂቃ ድረስ ይፋ እንዳላደረገ ይታወቃል። የዛሬ አመት ለተፈጠረው ግድያ በተመሳሳይ መልኩ ከምርመራው በፊት ጣቱን ሌሎች ላይ ቢቀስርም፣ የሆነው ግን ሌላ ሆኖ የተገኘው። ውጤቱም እስከአሁኗ ደቂቃ ድረስ ለህዝብ አልተነገረም። በመካከላቸው ለተፈጠረው አለመግባባት ተጨማሪ ቤንዚን ሆነ አገለገለ ይበልጥ መካረር ውስጥ ከተታቸው እንጂ የፈየደው ነገር አልነበረም። ዛሬም ምርመራ ከመካሔዱ በፊት ውንጀላው አንድ ቡድን ላይ (ህወሓት ላይ) አድርጎ እያደነ የሚያስረው ደግሞ ሌላ ቡድንን (የእነ ጀዋር) ነው። ህወሓት/ግብጽ ከሆነ ሀጫሉን የገደለው ኦሮሚያ ላይ የብልጽግና ውጋት የሆኑ የፖለቲካ ድርጅቶችን የሚመሩ የፖለቲካ መሪዎችና ጋዜጠኞች ለምን እየታድኑ ታሰሩ?

ተጣርቶ እስኪታወቅ ድረስ መላምት መደረት የሚቻል ከሆነ፣ ከአጫሉ ግድያ በስተጀርባ ህወሓት፣ የኦሮሞ ብሔርተኞቹ፣ የግብጽ ተላላኪዎች ሊኖሩ ከቻሉ፣ አብይ ራሱ ሊኖር የማይችልበት ምክንያት ምንድን ነው? እስኪ በዝርዝር እንመልከተው። በአባይ ግድብ ዙሪያ በተደጋጋሚ እንዳየነው እርሱ የተካፈለበት ድርድር፣ የአገርን ሉአላዊነት አሳልፎ የሚሰጥ ነበር። በመጀመሪያ አሜሪካና የዓለም ባንክ አደራዳሪ እንዲሆኑ የተስማማው አብይ ነው። ሲቀጥል በሁለት ሳምንት ውስጥ ስምምነት ላይ መደረስ አለበት፣ ስምምነት ላይ ከመድረሳችን በፊት ግድቡን መሙላት አንጀምር ብሎ ግብጽን ያስፈነጠዘ ስምምነት የፈጸመው አብይ ነው። አጫሉ በተገደለበት እለት ደግሞ፣ ግድቡን የመሙላት ሂደት የመብት ጉዳይ ሳይሆን፣ የጦርነት ጉዳይ ይመስል፣ የጸጥታው ምክር ቤት አጀንዳ እንዲሆን ያደረገው አብይ ነው። እዛ ደግሞ ምን አይነት ስምምነት አድርጎ እንደመጣ አናውቅም። ምናልባትም ከዛ አጀንዳ ለማስቅየስ የተደረገ፣ ብሎም አገርን በማበጣበጥ፣ ግድቡን የመሙላት ሂደት ለማዘግየት የተቀነባበረ ሴራም ሊሆን ይችላል። በነገራችን ላይ በነዚህ ጉዳዮች ጀዋር ሲያራምድ የነበረው አቋም፣ እንደ አንድ ፖለቲከኛ ሳይሆን እንደ አንድ አገር መሪ ነበር። እንዲያውም መጨረሻ ላይ፣ በዲፕሎማሲው ረገድ ደህና ድል እያገኘን የነበረውን ሁኔታ የቀለበሰው፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ስራውን እንዳይሰራ ስለተደረገ ነው፣ የሚል ስሞታ አሰምቷል። አብይን በአገር ጉዳይ የማያምነው መሆኑ፣ ልክ ብዙዎቻችን የታዘብነውን አይነት ክህደቶችን የታዘበ መሆኑን የሚያሳይ ፍንጭ ጽፎ ነበር። በእርግጥ ግብጽን አልጎዳም ብሎ በማያውቀው ቋንቋ ደጋግሞ የማለውና የተገዘተው ማን እንደሆነ ሁሉም ያውቃል።

ይህን ግድያ አብይ ከግብጽ ጋር ያለውን ጉዳይ ለማለዘብ ብቻ ሳይሆን፣ ተቀናቃኞቹን ለመስበርም እየተጠቀመበት ያለ ይመስለኛል። ከላይ እንዳልኩት ኦሮሚያ ላይ፣ ሰማይ ምድሩ ቢገለበጥ፣ በነጻ ምርጫ ሊያሸንፋቸው የማይችሉ ተቀናቃኞቹ ለማሰር ተጠቀሞበታል። የኦሮሞ ተቀናቃኞቹን ከሰበረ ብኋላ በሙሉ ጉልበት ፊቱን ወደ ህወሓት ማዞር ነው ስሌቱ። ያው የጅል ስሌት ነው። ፊቱን ወደ ሰሜን ከማዞሩ በፊት፣ ኦሮሚያ ላይ በማሰው ጉድጓድ ራሱን ያገኘዋል። የት ድረስ እንደሚያዛልቀው እንኳን በደንብ ያሰላው አይመስልም። ለእርሱ ታማኝ የሆኑ አንድ ሁለት ቀበሌ ማተራመስ የሚችሉ ልዩ ሃይሎች ቢኖሩትም፣ የሚያስመካና ልትተማመንበት የምትችል ጉልበት ያላቸው አይደሉም። ሁሉም የተነሳባቸው እለት ድራሻቸው አይገኝም።
ከዚህ ሁሉ ግን፣ ከተቀናቃኞቹ ጋር ያለውን ችግር በድርድርና በውይይት ቀድሞ ፈትቶ ወይም ለመፍታት ሞክሮ ቢሆን ኖሮ ይህ ሁኔታ ሊፈጠር ይችል ነበር? አይመስለኝም። ምክንያቱም እርሱም ሆኑ ሌሎቹ ችግራቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ፣ በሰለጠነ መንገድ ከፈቱ የዚህ አይነት ሴራ ውስጥ መግባት አያስፈልጋቸውም ነበር። ለዚህ እነ ጀዋርም፣ ህወሓትም ሌሎችም ዝግጁ መሆናቸውን በተደጋጋሚ በግልጽ ሲናገሩ ሰምተናል። ለጥሪው ጆሯቸውን የቆለፉበት አብይና የአብይ ድርጅት ብቻ ናቸው። ይህን ባለማድረጉ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል በሴራ ፖለቲካ ያለ እድሜው መሞት የማይገባው ወጣት እንዲሞት ሆነ። በዛ የተነሳም ሌሎች በርካታ ንጹሃን ዜጎች እንዲሞቱ፣ እንዲቆስሉ፣ አገሪቱ ሌላ ቀውስ እንድታስተናግድ (እግዜር ይሁናትና!) ምክንያት ሆነ። ታድያ ማነው ለዚህ ተጠያቂው? ማን ነበር ይህን ማስቀረት ይችል የነበረው? በማን ውሳኔና እጅ ነበር?

አብይ፣ ሰልፊሽና የስልጣን ጥመኛ በመሆኑ ብቻ፣ አገሪቱን ከማቀራረብ ይልቅ፣ የባሰ ጽንፍ ነው ያስያዛት። ህወሓትን ሲታገሉ መቀራረብ ጀመረው የነበሩትን፣ ያራራቃቸውና ጽንፍ ያስያዛቸው የአብይ መንግስት ነው። ይህንን ቀዳዳ ተጠቅመው የውጭ ሃይሎች አገራችን ውስጥ ሴራ ቢሞክሩ እንኳን አይፈረድባቸውም። የሚያራርቅ እንጂ የሚያቀራርብ መሪና አሰራር እንደሌለን ይታወቃል። በድጋሚ ላንሳውና በድርድር ልዩነቱን ቀርፎ ቢሆን ኖሮ፣ የውጭ ሃይል አገራችንን የማተራመስ እድል ይኖረዋል? ግብጽ ብትሞክር እንኳን፣ መግባባት ካለ፣ በጋራ ያከሽፉት ነበር። ታዋቂ ሰው/ፖለቲከኛ ገድለው አመጽ ለመቀስቀስ ቢሞክሩ፣ ታዋቂ ሰዎች (ተፎካካሪዎች) በጋራ ቆመው፣ ተሰሚነታቸውን ተጠቅመው፣ ህዝባቸውን ያረጋጉ ነበር። አሁን ባለበት ሁኔታ ግን ይህ የሚቻል አልሆነም። ምክንያቱም ሁሉንም ነገር በራሱ መንገድ ብቻ ከማስተናገድ ውጭ ሌላ ነገር ስለማያውቅ።

ሲጠቃለል ከሀጫሉ ግድያ በስተጀርባ ያለው ሀይል ማንም ይሁን ማን፣ የመንግስት ተጠያቂነት ጎልቶ ይታየኛል። ገዳዮ ምንም ፖለቲካል ሞቲቭ የሌለው አንድ ተራ ሰው (ለምሳሌ የምኒሊክ አምላኪ) ሆኖ ቢገኝ እንኳን፣ አገሪቱን እዚህ ቀውስ ውስጥ የከተተው (ምናልባትም የከፋ ቀውስ ውስጥም ሊከታት የሚችለው) ማን በፈጠረው ችግር ምክንያት እንደሆነ ለሁላችንም ግልጽ ነው። ደጋግመን ድርድር፣ ውይይት፣ ድርድር፣ ስንል የነበረው ለዚህ ነው። አሁንም አገሪቱ ከዚህ ውጭ ሌላ መውጫ ቀዳዳ የላትም።

በመጨረሻ አንድ አቋሜን ግልጽ ላድርግ፣ ከሀጫሉ ግድያ በስተጀርባ የነጀዋር እጅ አለበት ብዬ የማላምነውን ያህል፣ የተደራጀ የአማራ ፖለቲከኞች ቡድንም ይኖራል ብዬ አላምንም። እነ ጀዋር አመጽ መቀስቀስ ከፈለጉ፣ ሀጫሉን መግደል አያስፈልጋቸውም። የአመንስቲ ሪፖርት የፈጠረውን አጋጣሚ ተጠቅመው ማቀጣጠል ይችሉ ነበር። ሀጫሉ ካስፈለጋቸውም አብሯቸው እንዲያቀጣጥል ማድረግ ይችሉ ነበር። እንዲህውም ነፍጠኛ የምትሏቸው የተደራጁ የአማራ ብሔርተኞችም ከዚህ ጀርባ አይኖሩም፣ ምክንያቱም የምኒሊክ ስም ከመጥፋት በላይ (ያውም ያልተለመደ አይደለም) የሚያሳስብ ዘርፈ ብዙ ችግር አለ። ለማይረባ ነገር ያን የመሰለ አርቲስት ገድሎ፣ የባሰ ጥፋትና ኪሳራ እንጂ ጥቅም እንደማይገኝ አያውቁም ለማለት አልደፍርም።

 

ሰ.ነ.

ወደ አምባገነናዊ ስርዓት መመለስ አገር ያሳጣል

ለዚህ  ጽሁፌ መነሻ ምክንያት ወደ ሆነኝ ነጥብ ልምጣና የኢህአዴግ አልጋ ወራሽ የሆነው ብልጽግና ልክ እንደትላንቱ ዛሬም በተመሳሳይ ጎዳና እየገሰገሰ ይገኛል። ኩንትራቱን ሊጨርስ እየተቃረበ ያለው ጠ/ሚ/ር አብይ አሕመድ፣ በኢህአዴግ ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በአሸናፊነት ተወጥቶ ስልጣኑን ለማደላደል ሲል ብልጽግናን የመሰረተበት ሒደት፣ ድርጅቱን ለማጠናከርና አባላትን ለማፍራት እየተጓዘበትና ያለው መንገድ ከቀድሞ የኢህአዴግ ባህል ምንም የተለየ አይደለም። ኢህአዴግ የቀድሞ ስሙን ብቻ ቀይሮ በህይወት አለ። ልዩነቱ የቀድሞ ታጋዮች ኮትኩተው ባሳደጓቸው ካድሬዎች በፖለቲካ ጌም መሸነፋቸው ብቻ ነው። ሰዎቹ ተሸነፉ እንጂ የዘረጉት ባህል አልተሸነፈም። ካድሬዎቹ ከህወሓት ካድሬዎች ውጪ ቀሪዎቹ የነበሩት ናቸው። የሚተዳደሩት በለመዱትና በኖሩበት የድርጅት ባህል ብቻ ነው። ለዚህም ነው ብልጽግና ከኢህአዴግ የተለየ ባህል ሊኖረው የማይችለው።

ጠ/ሚ/ሩ በህዝብ ይሁንታ፣ በተሰጠው የሁለት አመት የስልጣን ገደብ ቀድሞ የገባውን ቃል አጥፎ፣ የዴሞክራሲ ተቋማትን ሳይገነባ፣ ነጻና ገለልተኛ ምርጫ ሳያካሒድ፣ ስልጣን በሰላማዊ መንገድ በህዝብ ለተመረጠ አሸናፊ ፓርቲ ማስተላለፍ የሚችልበትን እድል ሳይፈጥር፣ በማንኛውም መንገድ ስልጣን ላይ ለመቆየት የሚያስችሉትን አማራጮች እየዘረጋ ቆይቷል። አንዱ መንገድ የቀድሞ አጋሮቹን ገፍትሮ በአዲስና ታማኝ ካድሬዎች መተካት ነው። እኔ አሻግራችኋለው ከማለት ስልጣን ላይ ካልቆየሁ መታሰራችን ነው ወደ ማለት ተሸጋግሯል። ይህ አፍሪካ ነው፣ ምርጫ ማጭበርበር ብርቅ አይደለም ማለቱም ተሰምቷል። አንድ ሰሞን መተካከት የሚባል የፖለቲካ ዲስኩር ተፈጥሮ ነበረ። አቶ መለስ የቀድሞ ጓዶቹን በመተካካት አሰናብቶ፣ በአዲስ ሀይል ተካቸው። እኔም በቅቶኛል ስልጣን ለአዲሱ ትውልድ አስተላልፋለሁ ሲል ቆይቶ፣ ባለቀ ሰዓት ድርጅቴ መርጦ አዲስ አደራ ስለጣለብኝ፣ ግዴታዬን መወጣት አለብኝ አለ። በ99.96% አሸነፍኩ ብሎ የለየለት አምባገነን ሆኖ ብቅ አለ።

ዛሬም ዶ/ር አብይ እየተጓዘበት ያለው መንገድም ተመሳሳይ ነው። አሻግራለሁ ሲል ቆይቶ፣ ሌላ መሪ ማን አለ እስከማስባልና ዛሬ ስልጣን ላይ ካልቆየን መታሰራችን ነው የሚል አቋም እስከማራመድ ድረስ ዘልቋል።

ምርጫውን መራዘም አለበት የሚል ዘመቻ የተከፈተው አምና ነበር። ከተራዘመ የቅቡልነት ጥያቄ ሊነሳ እንደሚችል ሲገለጽ፣ ነሓሴ እንደሚካሔድ ተገለጸ። ውሳኔው ምርጫው በግፊት የሚራዘምበትን ሰበብ ለመፍጠር ያለመ ይመስል ነበር። የኮቪድ ወረርሽኝ ሲከሰት፣ ጥሩ አጋጣሚ ሆነለትና ምርጫው እንዲራዘም ተደረገ። ምርጫው መራዘሙ ብቻ ሳይሆን፣ ያልተገደበ ስልጣን የሚሰጠው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አሳወጀ። አዲስ የአፈና መርበብ ተዘረጋ። ስልጣን ላይ በጉልበት ለመቆየት ርብርቡ ቀጥሏል።

ይህ በዙርያው ላሰባሰባቸው ኪራይ ሰብሳቢዎች ትልቅ ሲሳይ ነው። ከህዝብ ተነጥሎ በካድሬና በድርጅቱ ሰዎት መተማመን ከጀመረ፣ መዝረፍ የፈለገ አሁን እንደልቡ ይዘርፋል። እንደድሮ በግፍ ራሱን ማዝናናት የሚያስፈልግ ካለም አሁን ያን ማድረግ ይችላል። ምክንያቱም ሰውዬው ከህዝብ ተነጥሏል። የሚፈራው ነገር እንዳይደርስበት ካድሬዎቹን ሸክፎ መያዝ አለበት። ሲሰርቁና ግፍ ሲፈጽሙ እየቀጣ ካድሬን ሸክፎ ማቆየት ደግሞ አይቻለውም። ስለሆነም ነጻ ይለቃቸው፣ ከቁጥጥሩ ውጭ ናቸው።

ትላንት በኮረና ስም፣ ትንሽ ሰብሰብ ያሉ ሰዎችን ለመበተን ሲባል፣ ወጣቶችን ገደሉ። እንደገና ቤት አፍርሰው ደግሞ በርካቶችን ለበሽታው ማጋለጣቸው አልቀረም። ከእንግዲህ እንዲህ አይነት ዝብርቅርቁ የወጣን ነገር ማስታረቅም፣ ማረምም አይቻለውም ጋሽ አጃግሬ። ያለው አማራጭ በስልጣኑ እስካልመጡበት ድረስ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ማለፍ ነው።

አብይ ብዙ ጊዜ ስቷል። አንኳር ስ ህተቶቹ ግ ን ሁለት ናቸው። አንደኛ ተቋማትን መገንባትና ራሳቸውን ችለው እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ ሲገባው፣ እርሱን የሚያወድሱና በስልጣን ላይ ሊያቆዩት የሚሹ አጨብጫቢዎችን አፈራ። ሁለተኛ ስልጣን እየጣፈጠችው ስትሔድ ከህዝብ እየራቀ ሔደ፣ አምባገነናዊ ባህሪ እየተላበሰ ሔደ። አሁን መፍራት ጀመረ። ፍራቻው አገርን እንዳያሳጣን እፈራለሁ።

ሊበራላይዜሽን?መለስ ዜናዊ እና አብይ አሕመድ

መለስ ዜናዊን በብዙ ምክንያት እቃወመው ነበር። ይህን ከፋፋይ የዘር ፖለቲካ ማምጣቱ፣ ስልጣን ላይ ሙጭጭ ማለቱ፣ ስልጣን ላይ ለመቆየት የተጓዘበት ርቀት(የሚመራው ድርጅት በሀሳብ ድርቅ እስኪጠቃ ድረስ የተማረ ሰው የማያስጠጋ መሆኑ)፣ ወዘተ ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው። ማንም የማይክደውና የሚደነቅበት ብቃት ደግሞ ነበረው። የኢኮኖሚክስ እውቀቱ ከባድ ሚዛን (ወርልድ ክላስ) ነበር።

መለስእነ ጆሴፍ ስቲግልዝ (በኢኮኖሚክስ ኖቤል ተሸላሚዎች) ፣ እነ ፒተር ጊልስ (አዋርድ ዊኒንግ ጋዜጠኞች)፣ እነ አሌክስ ዴ ቫል እና ሌሎችም ብዙ ግዜ መስክረውለታል። መጽሀፋቸው ላይ አንድ ምእራፍ ሙሉ ሰጥተው ትንታኔውን ከትበውታል፣ አድናቆታቸውን ችረውታል። መለስ የተደነቀበት የኢኮኖሚክስ እይታ “በድሀ አገር ሙሉ በሙሉ ነጻ ገበያ መፍቀድ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል”፣ “ሉአላዊነታቸውን ያሳጣቸዋል”፣ “በውጭ ባለሀብቶችና ኢንቨስተሮች ቁጥጥር ስር ይወድቃሉ” በሚለው አቋሙ ነው። በኢትዮጵያ ይህን ከምፈቅድ፣ እንደኤሊ ቀስ እያልን ብናዘግም እመርጣለሁ። የሚል ጽኑ አቋም ነበረው። በተለይ ጆሴፍ ስትግልዝ ከባንክና ከመሬት ሊበራላይዜሽን ጋር በተያያዘ በአንዲት ሌሊት ብዙና ጠንካራ የመከራከሪያ ጭብጦችን ማንሳቱ በአግራሞት ያወሳል። በተለይ ከኢስት ኤሽያ ክራይስስ ብዙ ምሳሌዎችን በመጥቀስ፣ ካገሩ ሁኔታ ጋር በማያያዝ አስደማሚ ክርክሮችን ማንሳቱን በአድናቆት መጽሀፉ ላይ ከትቦታል።

ዛሬ ሴንሲብል የሆኑ የአሜሪካ ምሁራን ጆሴፍ ስቲግልዝን ጨምሮ የነጭ ካፒታሊዝም ተቃዋሚዎች ናቸው። ዘ ኢኮኖሚስት በተደጋጋሚ የሚጽፋቸውን አርቲክሎች ላነበበ፣ የስካንዲኔቭያን ዓይነት ኢኮኖሚክ ሞዴል ተግባራዊ ለማድረግ የከጀሉ ይመስላል። በተደጋጋሚ በሚያስተዋውቁት አንድ የሽፋን ገጻቸው “ሶሻሊዝም የነገ ርእዮተ ዓለም” የሚል ምጸት ይዘው ቀርበዋል። የአየር ለውጥ የሚያሳስባቸው ኢኮኖሚስቶችና ፖለቲካል ሳይንቲስቶች፣ እንደዚሁም የአካባቢ ጥበቃ አድቮኬሲ ቡድኖችና ፈላስፋዎች እንደነ Naomi Klein ፣ Noam Chomsky፣ Slavoj Žižek እና የመሳሰሉት አለምን ለማዳን ከነጭ ካፒታሊስት (ነጻ ገበያ) ስርዓት መውጣት አለብን፣ ሲሉ ላንቃቸው እስኪነቃ ድረስ ያቀነቅናሉ።

በአንጻሩ አብይ አሕመድ ወደ ስልጣን ከመጣ ጀምሮ ማንም ሳይመርጠውና ይሁንታውን ሳይሰጠው፣ የኢትዮጵያን ህዝብና አገር ወክሎ የሚወስናቸው ውሳኔዎችና የሚፈጽማቸው ውሎች፣ እስከዛሬ ድረስ መለስና ኢህአዴግ አስከብረዉት የነበረ የኢኮኖሚ ሉአላዊነት የሚያስደፍር ነው። ይህ ድርጊቱ የአገሪቱን ሉአላዊነት በረጋግዶ አሳልፎ ከመስጠት ተለይቶ ሊታይ አይችልም። የአለም ካፒታሊስት ስርዓት አራማጅ ወደ መሀል እየመጣ ባለበት፣ በቅይጥ ኢኮኖሚ ስርዓት(ቅድሚያ ላገር ውስጥ ባለሀብት ቦታና ትኩረት በመስጠት) ኢኮኖሚያቸውን እያሳደጉ ያሉ አገራት በተበራከቱበት፣ አብይ ብቻውን ወደዚህ መንደር የሚያደርገው ግስጋሴ ከእንጭጭ ጭንቅላት የመነጨ ከሰራቸውና እየሰራቸው ካሉ ክፋቶች ሁሉ የከፋ ተግባር ነው።

አዎ ኢህአዴግ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ያስመዘገበው እድገት አለ። ከሚያገኘው ከፍተኛ ድጋፍና ብድር ጋር የማይመጣጠን ዝቅተኛ እድገት ቢሆንም የኢኮኖሚ ዕድገት ነበረ። ኢህአዴግ የሚወገዘው እድገት ባለማስመዝገቡ ሳይሆን፣ ህዝብን የዛ እድገት ተጠቃሚ አለማድረጉና የተመዘገበው እድገት ለጥቂቶች ብቻ የተደፋ ዳቦ በማድረጉ ነበረ። በሌላ አነጋገር በግልጽም ይሁን በድብቅ እየዘረፉ ራሳቸውንና በዙሪያቸው ያሉትን ብቻ እየጠቀሙ ሌላውን አድኽይተው ለመግዛት መሞከራቸው ነበር ትልቁና ዋነኛ ስህተታቸው። ይህን ስህተት አብይ በቀላሉ ማረም ይችል ነበር። ገበያውን በረጋግዶ ለውጭ ኮርፖሬሽኖች ልስጥ ማለት አያስፈልገውም ነበር።

ህዝብን የእድገቱ ተጠቃሚ ለማድረግና የተሻለ እድገት እንዲኖር ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለበት አሰራር መዘርጋት ነበር የሚያስፈልገው። በሌላ አነጋገር በነጻ ገበያ ስም ያገር ሀብት ከመቸብቸብ በፊት የህግ የበላይነት ማስከበር መቅደም ነበረበት። ሙስኞችን ለህግ ማቅረብ፣ የህዝብ ንብረት ማስመለስ፣ ነጻ ሚድያ፣ ነጻ የፍትህና የኦዲት ስርዓት መዘርጋት ወዘተ በማስቀደም ህዝብን ተጠቃሚ ማድረግ መቅደም ነበረበት። በሒደት የአገር ውስጥ ባለሀብት አቅም ካካበተ ብኋላ እና ዛሬ ለውጭ ባለሀብት ሊበራላይዝ እየተደረጉ ያሉ የመንግስት ኩባንያዎችን በጨረታ ተወዳድሮ የማሸነፍና የመግዛት አቅም ሲፈጥር ነበር፣ ዛሬ እየተወሰደ ያለው የሪፎርም እርምጃ ሊወሰድ ይገባ የነበረው። በሌላ አነጋገር፣ ለአገር ውስጥ ባለሀብት ቅድሚያ በሚሰጥ ፕሮቴክሽኒስት ፖሊሲ ነው ነጻ ገበያ መለማመድ የሚኖርብን።

ከፈረሱ በፊት ጋሪው ቀድሟልና ወደ ተግባራዊነቱ ከመሸጋገሩ በፊት የሚመለከታቸው አካላት፣ ዩኒላተራሊ እየተወሰነ ባለው በዚህ ሰውዬ አካሔድ ላይ ልጓም ቢጤ ቢያኖሩለት ይመከራል።