ምን በጀን? በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የቀረበ አስተያየት

ታላቁ ንቅናቄና የህውሓት ግብረመልስ

በኔ እምነት የኢትዮጵያውያን የነጻነት ንቅናቄ እማይቀለበስ ደረጃ ላይ ደርሷል። ከዚህ ብኋላ መሰረታዊ የስርዓት ለውጥ ሳይመጣ ህዝቡ ከንቅናቄው ያፈገፍጋል የሚል እምነት የለኝም። ለዚህም ነው ታላቁ ንቅናቄ ለማለት የደፈርኩት። በሌላ በኩል ደግሞ ላለፉት 25 ዓመታት ካየነውና ከራሳቸው አንደበት ከሰማነው፡ ህውሓት ስልጣኑን በዚህ መንገድ በቀላሉ ይለቃል ብዬ አላምንም። ዛሬም ድረስ በነ ዓይጋ ፎረምና ትግራይ ኦን ላይን ላይ የምናነባቸው ነገሮች “እኛ ካልመራን አገሪቱ ትበታተን” የሚል እንድምታ ያላቸው ጽሁፎችን ነው። ይህም የሚያሳየው የፖለቲካ የበላይነቱን እንደተቆናጠጡ በስልጣን ላይ ለመቆየት አሉ የተባሉትን አማራጮች በሙሉ አሟጠው እስከመጠቀም ድረስ ሊዘልቁ እንደሚችሉ እንጂ ለህዝብ ጥያቄ ጆሮ አይሰጡም። Read more

የኢትዮጵያ ጉዞ ወዴት? የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ! (ክፍል 1)

  • የኢትዮጵያ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተቋማት (institutions) በአንድ ወቅት ከአውሮፓ አገራት ጋር ተመሳሳይ ነበሩ። ኢትዮጵያ ከአውሮፓ አገራት ጋር ተነፃፃሪ ቦታ ላይ ነበረች።
  • በመቶዎች የሚቆጠሩ ማንነቶች ከስመው ጥቂት ወጥ የሆኑ ማህበረሰቦች ብቻ ዘመናዊቷን አውሮፓ መስረተዋል። አሁንም ግስጋሴው ወደ አንድነት ነው።
  • አውሮፓ የተከተለችው መንገድ ሌሎች በርካታ አገራት ተከትለውታል። ወይም ቀድመው ሄደውበታል (ለምሳሌ ቻይና)።  ኢትዬጵያ ይህን መንገድ አልተከተለችም። ለምን?
  • የኢትዮጵያ የተለየ መንገድ እንድምታው ምንድን ነው? እነዚህንና ሌሎች ነጥቦችን የሚዳስስ ጽሁፍ በሁለት ክፍል ተዘጋጅቷል። ክፍል አንድ እንሆ። መልካም ንባብ!

Read more

ዕድገት: በቻይናና ኢትዮጵያ (ክፍል 1)

«ታላቁ ዝላይ» ና የወረቀት ላይ ዕድገት በ1958 እኤአ የቻይናው መሪ ማኦ ዜዱንግ (Mao Zedong) «ታላቁ ዝላይ» (The Great Leap Forward) የተባለ የልማት ዘመቻ ቀርጾ አገሪቱን በዕዝ ኢኮኖሚ (command economy) ከድህነት…