ምን በጀን? በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የቀረበ አስተያየት
ታላቁ ንቅናቄና የህውሓት ግብረመልስ
በኔ እምነት የኢትዮጵያውያን የነጻነት ንቅናቄ እማይቀለበስ ደረጃ ላይ ደርሷል። ከዚህ ብኋላ መሰረታዊ የስርዓት ለውጥ ሳይመጣ ህዝቡ ከንቅናቄው ያፈገፍጋል የሚል እምነት የለኝም። ለዚህም ነው ታላቁ ንቅናቄ ለማለት የደፈርኩት። በሌላ በኩል ደግሞ ላለፉት 25 ዓመታት ካየነውና ከራሳቸው አንደበት ከሰማነው፡ ህውሓት ስልጣኑን በዚህ መንገድ በቀላሉ ይለቃል ብዬ አላምንም። ዛሬም ድረስ በነ ዓይጋ ፎረምና ትግራይ ኦን ላይን ላይ የምናነባቸው ነገሮች “እኛ ካልመራን አገሪቱ ትበታተን” የሚል እንድምታ ያላቸው ጽሁፎችን ነው። ይህም የሚያሳየው የፖለቲካ የበላይነቱን እንደተቆናጠጡ በስልጣን ላይ ለመቆየት አሉ የተባሉትን አማራጮች በሙሉ አሟጠው እስከመጠቀም ድረስ ሊዘልቁ እንደሚችሉ እንጂ ለህዝብ ጥያቄ ጆሮ አይሰጡም። Read more
