, ,

ዶ/ር አብይ አሕመድ በጣልያን ቦለኛ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሊሆን እንደሚችል ተገለጸ

ከህዝብ እይታ ለበርካታ ሳምንታት ርቀው የቆዩት ዶ/ር አብይ አሕመድ አሊ፣ ትላንትና ማታ በአንድ የአውሮፕላን አምቡላንስ ከአዲስ አበባ/ፊንፊኔ ወደ ጣልያን ሳይጓዙ እንዳልቀረ ተገለጸ።

የአውሮፕላን አምቡላንሱ ዛሬ በጣልያን ቦለኛ ማረፉ ተረጋግጧል።

ትላንትና ማታ የጠቅላይ ሚንስቴሩ ጽህፈት ቤት በዶ/ር አብይ አሕመድ ጤንነት ዙሪያ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሀሳት ነው የሚል መልዕክት በትዊተር ገጹ ማስተላለፉ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ተንታኝ የሆኑት ዶ/ር በሽር ሀሺ ዩሱፍ፣ ዶ/ር አብይ ከጥቂት ቀናት በፊት ከሱዳን ዲፕሎማቶች ጋር ሲወያዩ ታመው እንደነበረ መረጃው ደርሶኛል ይላሉ።

የሰላም ሚንስቴር ሚንስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በበኩላቸው ዶ/ር አብይ በስራ ገበታቸው እንደሚገኙ በፌስቡክ ገጻቸው ገልጸዋል።

የአፊርካ ቀንድ የፖለቲካ ተንታኝ የሆኑት ራሽድ አብዲ ዶ/ር አብይ ከህዝብ እይታ መራቃቸው ያልተለመደ ሆኖባቸዋል።

አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ዶ/ሩ የፖለቲካ ሴራ እየሸረቡ ሊሆኑ እንደሚችል ይገምታሉ። ሆኖም ሌሎች በርካቶች አገሪቱ በሁሉም አቅጣጫ ከራሷና ከአጎራባቾቿ ጋር ጦርነት በከፈተችበት ወቅት እንዲህ ያለ ዜና ይበልጥ ቀውሱን የሚያባብስ እንጂ የሚበጅ ባለመሆኑ፣ ዶ/ሩ ካሉበት በቀጥታ ስርጭት ለህዝብ መልዕክት በማስተላለፍ አገሪቱን ማረጋጋት ይኖርባቸዋል ይላሉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በማህበራዊ ሚድያ አንዳንድ ደጋፊዎቻቸው በብልጽግና ውስጥ ክፍፍል መፈጠሩን ይናገራሉ። የዶ/ሩ ደጋፊ አቶ ስዩም ተሾመ የመታመማቸውን ዜና ተከትሎ ትላንትና ማታ በፌስቡክ ገጻቸው ባሰራጩት መልዕክት “በአዲስ አበባ (ፊንፊኔ) እና በኦሮሚያ አመጽ ሊቀሰቀስ እንደሚችል መረጃ ደርሶኛልና ለሚመለከታቸው መልዕክቱን አድርሱልኝ” ብለዋል። (ያ መልዕክት በማግስቱ ከገጻቸው ተነስቷል።) ሌሎች በርካታ የዶክተሩ ደጋፊዎች ዶክተሩ በጤናና በመደበኛ የስራ ገበታቸው እንደሚገኙ በገጾቻቸው አስፍረዋል።

የኢንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ሚ/ር ዶምኒክ ራብ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከዶ/ር አብይ ጋር መነጋገራቸውን በትዊተር ቢገልጹም በምስል አብረው የታዩት ከም/ጠ/ሚ/ር ደመቀ መኮነን ጋር መሆኑ ብዙዎችን አነጋግሯል።

አቶ ደመቀ መኮነን የቀድሞ የብአዴን፣ የዛሬ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አመራር ሲሆኑ፣ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሚንስትርነት ማዕርግም ደርበው መያዛቸው ይታወቃል።

አቶ ደመቀ ቀደም ሲል በመተከል ይታይ የነበረው ግጭት፣ መፍትሔው ምንድን ነው ተብለው ሲጠየቁ፣ አማራን ከማስታጠቅ ውጪ ሌላ መፍትሔ የለውም በሚለው አወዛጋቢ ምላሻቸው ይታወቃሉ።

ዶ/ር አብይ ለመጨረሻ ግዜ ለህዝብ በአካል የታዩት በመተከል ከአገር ሽማግሌዎች ጋር ሲወያዩ እንደነበር ይታወሳል። በተወያዩ በማግስት በተነሳ ግጭት ከ200 በላይ ሰዎች ተገድለው ማደራቸው በተለያዩ የሚያድያ አውታሮች ተዘግቦ ነበር።

በመተከል በቀጥታ ከሚጋጩት ከአማራና ከጉምዝ ብሔሮች ባሻገር በተዘዋዋሪ የኦሮሞ ታጣቂዎችና የሱዳን ምናልባትም የግብጽ እጅ ሊኖርበት እንደሚችል አንዳንዶች መላምታቸውን ያጋራሉ።

የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ላይ የከፈተው ጦርነት አገሪቱን ለተለያዩ ጥቃቶች አጋልጧታል፣ ህልውናዋንም አደጋ ላይ ጥሏል ይላሉ አንዳንድ ተንታኞች።

0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *