, , , ,

የትግራይ ህዝብ እና የህውሓት ግኑኝነት ነባራዊ ገፅታ

 ማሕበር ልምዓት ትግራይ /ማልት/TDA/

ይህ ድርጅት ሲቋቋም በተለይ በዳያስፖራ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች በጦርነት የተዳከመችዋን ትግራይ ተረባርበው እንዲያለሙ እድል ይስጣል በሚል ዓላማ ነበር። ነገር ግን በዚህ መንገድ ለበርካታ ዓመታት ከዳያስፖራ ተጋሩ፣ በውጪ አገራት የትግራይ ወዳጆች እና በአገር ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ ባለሃብቶች ከፍተኛ ገንዘብ የተሰበሰበ ቢሆንም መድረሻው ሳይታወቅ እንደተነነና ይህም ጥያቄ አስነስቶ እንደነበር ይታወቃል። በዚህ ምክንያት ድርጅቱ አንዴ እንዲፈርስ፣ ሌላ ጊዜ ተመልሶ እንዲቋቋም ሲደረግ ቆይቷል። ከጅምሩ ዓላማው ፖለቲካዊ እንጂ ልማታዊ ባለመሆኑ፣ አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ ዳግም እየመጣ የህዝቡን የልብ ትርታ የሚያዳምጡበት ሁነኛ የፖለቲካ መሳርያ ሆኗል። እንግዲህ የኔ ጥርጣሬ በዚህ ድርጅት የተሰበሰበው ገንዘብ፣ ብዙዎች እንደሚሉት በግለሰቦች ተመዝብሮ ድራሹ ጠፍቷል ሳይሆን ወደ EFFORT ወይም የህውሓት ካዝና ገብቷል የሚል ነው። ይህም ማለት በልማት ስም የሚሰበሰበው የመዋጮ ገንዘብ በራሱ ህውሓትን በማደለብ ጥቅም ላይ የሚውል ነው። የህውሓት የገንዘብ ምንጭ መሆኑ በራሱ የፖለቲካ መሳሪያ ቢሆንም ይህ ቀላሉ ጉዳይ ነው።

ከባለሀብት የተጀመረው ለማልት መዋጮ የመሰብሰብ አሰራር፣ ብኋላ የመንግስት ሰራተኛንና ተማሪውን የሚያሳትፍ እንዲሆን ተደርጓል። ከተማሪም ይሁን ከመንግስት ሰራተኛ የሚሰበሰበው ገንዘብ ያን ያህል የረባ ገንዘብ ባይሆንም በማልት ስም ህውሓት ለሚያቀርብላቸው ጥያቄ ባለሀብቶቹ፣ ሰራተኞቹና ተማሪዎቹ የሚሰጡት ምላሽ አወንታዊ ነው ወይስ አሉታዊ የሚለውን የሚለኩበት የፖለቲካ መሳሪያ ነው። አሉታዊ መልስ የሚሰጡት በርከት ያሉ እንደሆን “ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃዎችን ይወስዳሉ። እርምጃዎቹ ግለሰብ ተኮር ቅጣቶች በመሰንዘር ወይም systematic የሆኑ የአሰራር ለውጦችን በመከተል ሊፈጸሙ ይችላሉ። ማልት የህዝቡን የልብ ትርታ እያዳመጡ ከስር ከስር እርምጃ የሚወስዱበት መሳሪያ በመሆኑ ከEFFORT እና ከማረት ቀጥሎ ሶስተኛው የተዋጣለት የፖለቲካ መሳሪያ ነው ማለት ይቻላል።

ከነዚህ ሶስቱ ተቋማት በተጨማሪ እንደማንኛውም ክልል በትግራይ ሌሎች የማፈኛ መንገዶች ስራ ላይ ናቸው። 1ለ5 ጥርነፋ፣ የጸጥታ ሀይሉና መከላከያው በቁጥጥራቸው ስር መሆን፣ የፍትህ ተቋማትና ደህንነት በነሱ ስር መሆን፣ አስገድዶ አባል ማድረግ፣ አባል ላልሆነ ዜጋ የስራ ዕድልና ሌሎች ነገሮችን መከልከል፣ በአንጻሩ ደግሞ አባል ለሆነና ለሚደግፋቸው በተለያዩ መንገዶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ወዘተ በሌላው ክልል እንዳለ ሁሉ በዚህ ክልልም አለ። ለየት የሚለው ከላይ የተጠቀሱት ሶስቱ ተቋማዊ የአፈና መሳሪያዎች ናቸው።

5 replies
  1. Simon
    Simon says:

    እጅግ በጣም ገራሚ ትንተና ነዉ ሶሎሞን ያቀረብከዉ!!! እዉነታዉን ከነ ሙሉ ጭብጦቹ ስላቀረብከዉ በጣም ልትመሰገን ይገባል!!!

    Reply
  2. kedir Seid Mohammed
    kedir Seid Mohammed says:

    እንደኔ እምነት ይህ ጽሁፍ የትግራይ ህዝብ ያለበትን ተጨባጭ በጥልቀት የመረመረ፤ ምናልባትም ስለ ትግራይና ስለ ህዝቧ አስመልክቶ እስካሁን ካነበብናቸው ጽሁፎች በይዘትም በአቀራረብም የተለየ እንደሆነ አምናለው እናም ካለው ነባራዊ ሁኔታ ተነስቼም እውነት የትግራይ ህዝብ ምን ሁኔታ ላይ ነው ያለው፤ ከሌላው ማህበረሰብ ለየት ያለ የስርአቱ ታማኝ ደጋፊ እንዲሆን ያስቻለው፤ ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛላቸው ያደረገው እውነት ወዶ በፍቃዱ ነው ወይስ ከማያውቁት መልአክ የሚያውቁት ሰይጣን አይነት ነገር ሆኖበት ነው እናም የመሳሰሉ የብዙ ሰዎች ጥያቄ እዚህ ጽሁፍ ውስጥ መልስ እንደሚገኝባቸው አምናለው። ምናልባትም ያለንን የተሳሳተ እይታ ያስተካክላል ብየ ተስፋ አደርጋለው። ብዙዎቻችን ያለን አመለካከት ላይ ላይ ከሚታዩት አንድአንድ ማኒፈስቴሽኖች የዘለለ በጉዳዩ ላይ ጠለቅ ያለ ግንዛቤ ያለን መስሎ አይሰማኝም።

    መልካም ንባብ ፡)

    Reply

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *